“ምረጪ – ወይ እገልሻለሁ ወይ እደፈርሻለሁ”- በኢትዮጵያ ጦርነት ውስጥ የጥቃት ክሶች ተበራከቱ

በ ማይክል ጆርጂ ተፅፎ በ Horn Anarchists ተተረጎመ

Download PDF

ሃምዴት ፣ ሱዳን (ሮይተርስ) – ወጣቷ ቡና ሻጭ ተከዜ ወንዝ ላይ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር ከቤተሰቧ እና ወዳጆችዋ ጋር እንደነጠላት እና ለይቶ ወስዷት አስጨናቂ ምርጫ እንደሰጣት ትናግራች፡፡

የ 25 ዓመቷ ወጣት ከኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ተሰዳ አሁን ባለችበት በሱዳን ሃምዳዬት የስደተኞች ካምፕ ለሮይተርስ “’ምረጪ – ወይ እገልሻለሁ ወይ እደፈርሻለሁ’ አለኝ” ስትል ተናግራለች፡፡

በታህሳስ ወር ወደ ስደተኛ ካምፑ ስትመጣ ያከማት ሃኪም ቴዎድሮስ ተፈራ ሊሙህ እርግዝናን እና በጾታዊ ግንኙነት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለማስቆም ክኒን እንደሰጣት እና  ወደ ሳይኮቴራፒስት እንደ መራት ለሮይተርስ አረጋግጧል፡፡

ለሱዳን ቀይ ጨረቃ በበጎ ፈቃድኝነት እያገለገለ ያለው ዶ/ር ሊሙህ “ወታደሩ ጠመንጃ ደቅኖ አስገድዶ ደፈራት፡፡ ኮንዶም እንዳለው ስትጠይቀው ‹ለምን ኮንዶም ያስፈልገኛል?› ብሎ መለሰላት” ሲል ወጣቷ የነገረችውን ነግሮናል፡፡

አምስት የዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ዕርዳታ ድርጅት ሠራተኞች ተመሳሳይ የጥቃት ሪፖርቶች ከትግራይ እንደደረሷቸው ተናግረዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት በዚህ ሳምንት በክልሉ ውስጥ የሚደረጉ ወሲባዊ ጥቃቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ከቀረቡት “ከፍተኛ ቁጥር” ካላቸው የሚረብሹ ክሶች መካከል ዘመዶቻቸውን ለመድፈር የሚገደዱና መሰረታዊ አቅርቦቶችን ለማግኘት የግብረ ሥጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙ የሚገደዱ ሰዎች እንዳሉ የተ.መ.ድ የግጭቶች ወቅት ወሲባዊ ጥቃት ልዩ ተወካይ ያሳለፍነው ሃሙስ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግሥት እና ወታደራዊ መዋቅሩ ስለ አስገድዶ መድፈር ሪፖርቶች ከሮይተርስ ለተጠየቁት ጥያቄዎች ወዲያውኑ መልስ አልሰጡም። የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቀደም ሲል የመብት ጥሰቶችን ክደው ጣቶቻቸውን በአመፀኝነት ወደሚከሱት  የቀድሞ የክልሉ ገዥ ፓርቲ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ሕወሓት) ቀስረዋል።

የተባበሩት መንግስታት ልዩ ተወካይ ፕራሚላ ፓቴን በመግለጫው “በትግራይ ክልል በተፈጠረው ጠብ የሚሳተፉ አካላት ሁሉ በጾታዊ ጥቃት ወንጀል የዜሮ-መቻቻል ፖሊሲ እንዲወስዱ ጥሪዬን አቀርባለሁ” ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ሴቶችና ልጃገረዶች በተለየ ዒላማ የተደረጉ ሲሆን የህክምና ማዕከላት ለድንገተኛ የእርግዝና ማቋረጫ እና በጾታዊ ግንኙነት የሚተላለፉ ኢንፌክሽኖች ምርመራ ለማድረግ እየቸገራቸው መሆኑን መግለጫው ያሳያል።

ሮይተርስ የአስገድዶ መድፈር ክሶችን በገለልተኝነት ማረጋገጥ አልቻለም። አብዛኛዎቹ ሚዲያዎች ከትግራይ ታግደዋል ፣ የእርዳታ ድርጅቶች ተጎጂዎች ጋር ተደራሽ ለመሆን ተቸግረዋል፣ የግንኙነት መስመሮችም ለሳምንታት ተቋርጠው ቆይተዋል።

ዩኒፎርም ለባሽ አጥቂዎች 

ሮይተርስን ያነጋገረችው የ 25 አመቷ ሴት አጥቂዋ የኢትዮጵያ የፌደራል ጦር ዩኒፎርም ለብሶ እንደነበር ትናገራለች፡፡

አምስቱ የእርዳታ ሰራተኞች በበኩላቸው ሌሎች ሴቶች አጥቂዎቻቸው የአማራ ክልል ሚሊሻ ተዋጊዎች እና የኤርትራ ወታደሮች መሆናቸውን ገልፀዋል። ሁለቱም ከአብይ ሰራዊት ጋር ተባባሪ መሆናቸው ይታወቃል። ሮይተርስ ወጣቷን ያጠቃትን ሰው ማንነት መለየት አልቻለም።

የአብይ ቃል አቀባይ ፣ የትግራይ ጊዜያዊ ገዥ ፣ የክልሉ ዋና ከተማ ከንቲባ ፣ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ጦር ቃል አቀባይ በአስገድዶ መድፈር ክሶች ዙሪያ አስተያየት እንዲሰጡ ቢጠየቁም ወዲያውኑ መልስ አልሰጡም። ሮይተርስ የህወሓትን ተወካዮች ማግኘት አልቻለም።

የአማራ ክልል ቃል አቀባይ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በበኩላቸው በስልክ ለሮይተርስ “ስለዚያ ምንም መረጃ የለኝም” ብለዋል።

በደርዘን ከሚቆጠሩ የአይን ምስክር ቃለመጠይቆች፣ ዲፕሎማቶች እና ከአንድ የኢትዮጵያ ጄኔራል ተቃራኒ በሆነ መልኩ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የኤርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ውስጥ መኖራቸውን አስተባብለዋል፡፡

“ሴት ለምን ይደፈራል?”

በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በመቀሌ የተካሄደው የፀጥታ አስከባሪ ባለሥልጣናት ስብሰባ በኢትዮጵያ መንግሥት ቴሌቪዥን በተላለፈበት ወቅት፣ አንድ ወታደር ከተማዋ በፌዴራል ኃይሎች ከተያዘች በኋላም እየደረሱ ስላሉ ጥቃቶች ተናግሯል።

“ትናንት ተናድጄ ነበር። መቀሌ ከተማ ውስጥ ሴት ለምን ይደፈራል? በጦርነቱ ጊዜ ቢከሰት አያስደነግጥም ነበር … ግን ትናንትና ዛሬ የአካባቢው ፖሊሶች እና የፌደራል ፖሊሶች ባሉበት ሴቶች ይደፈራሉ።” ሲል ያልታወቀ ወታደር ተናግሯል።

የአከባቢው ባለሥልጣናት ወታደሮች መመርመር ወይም ለፍርድ መቅረብ ይችሉ እንደሆነ አስተያየት ቢጠየቁም ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጡም።

የስደተኞች ካምፕ ሀኪም የሆነው ቴዎድሮስ ስላያቸው ሌሎች ሁለት የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን ገልጻል። ከትግራይ ራውያን ከተማ ያመለጠች አንዲት ሴት በሯን ሲያንኳኩ የአማራ ልዩ ሀይል መሆናቸውን ስለለየቻቸው ሶስት ወታደሮች ትናግራለች። ቤቷ መግባት ስትከለክላቸው ሰብረው ገብተው ጥቃት እንደሰነዘሩባትም ተናግራለች።

በውቅሮ ከተማ ውስጥ የሚሰሩ የእርዳታ ሰራተኞች አንድ ሚስቱ በኤርትራዊ ወታደሮች ሲትደፈር ተንበርክኮ እንዲያይ ስለተገደደ ሰው ለሮይተርስ ተናግረዋል።

በዓዲግራት አንድ የህክምና ሰራተኛ በወታደሮች ቡድን  የተደፈሩ ስድስት ሴቶችን ማከሙን ገልጾ ከደፈሯቸው በኋላ እርዳታ ለማግኘት እንዳይሞክሩ እንዳስጠነቀቋቸው ተናግሯል። ከቀናት በኋላ ወደ ፊት መጥተው ያጋጠማቸውን ለመንገር ድፍረትን ቢያገኙም፣  እነሱን ለማከም የሚያስችሉ መድኃኒቶች እንዳልነበሩ ሃኪሙ ተናግሯል።

በመቀሌ ከተማ አንድ ሰው አንዲት የ19 አመት ታዳጊን መድፈር እንዲያቆሙ ወታደሮችን ሲለምን መደብደቡን ለሁለቱም ተጎጂዎች ህክምና ያደረገው የህክምና ባለሙያ ገልጿል። በመቀሌ የሚገኝ ኤልሻዳይ የሚባል የበጎ አድራጎት ድርጅት የአስገድዶ መድፈር ሰለባ ለሆኑ ሴቶች 50 አልጋዎች ማዘጋጀቱን ገለጿል።

‘እጅግ በጣም አስቸኳይ ፍላጎት’: ረሃብ ትግራይን እያስጨነቀ ነው

በካራ አና ተፅፎ በ Horn Anarchists ተተረጎመ
ናይሮቢ፣ ኬንያ Download PDF

    እጅግ ከደከሙ ስደተኞች፣ በአጨዳ ወቅት አፋፍ ላይ እስከ ተቃጠሉ ሰብሎች ድረስ ረሃብ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ከሁለት ወር በላይ ከዘለቀው ጦርነት በህይወት መትረፍ ለቻሉት ትልቅ ስጋት ጋርጦባቸዋል፡፡

ሰብአዊ እርዳታን ለማዳረስ የኢትዮጵያ መንግሥትን ተማፅነው ከገቡት የመጀመሪያ ግብረ ሰናይ ሠራተኞች ከወንዞች ውሃ እየጠጡ ስለተዳከሙ እና በተቅማጥ እየሞቱ ስላሉ ሕፃናት ይገልፃሉ፡፡ ሱቆች ከሳምንታት በፊት ተዘርፈው አልቀዋል፡፡ አንድ የአካባቢው ባለሥልጣን ታህሳስ 23 ቀን በተደረገ የመንግሥት እና የእርዳታ ሠራተኞች ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት የተራቡ ሰዎች “አንዲት ብስኩት” ጠይቀዋል፡፡ ከ 4.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ፣ የክልሉ ጠቅላላው ህዝብ ቁጥር ለማለት በሚያስችል ሁኔታ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይስፈልጋቸዋል ሲሉ የስብሰባው ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡ አንድ የትግራይ አስተዳዳሪ ታህሳስ 30 ቀን ባደረጉት ስብሰባ ላይ ያለ እርዳታው ባፋጣኝ ካልደረሰ “በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ሊሞቱ ይችላሉ” ሲሉ አስጠንቅቀው ነበር አሶሺዬትድ ፕሬስ ያገኛቸው ቃለ ጉባኤዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በረሃብ መሞት እንደጀመሩ ያመለክታል፡

የዶክተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ (ድንበር የለሽ ሐኪሞች ) ድንገተኛ ክፍል ሃላፊ የሆኑት ማሪ ካርመን ቪኖልስ “እጅግ በጣም አስቸኳይ ፍላጎት አለ – ሰብአዊ እርዳታን ለማፋጠን በእንግሊዝኛ ምን ተጨማሪ ቃላትን መጠቀም እንዳለብኝ አላውቅም – እኛ አሁን በምንነናገርበት ጊዜ በየቀኑ ህዝቡ እየሞተ ነው ፡፡” ሲሉ ለአሶሺዬትድ ፕሬስ ገልፀዋል

ነገር ግን የጦርነቱ መቀጠል ፣ የአንዳንድ ባለሥልጣናት ተቃውሞ እና የደረሰው ከፍተኛ ጥፋት የምግብ አቅርቦት ጥረቱ በሚፈለገው ልክ እንዳይሆን እንቅፋት ሆነዋል፡፡ ለ 4.5 ሚሊዮን ሰዎች 15 ኪሎግራም ራሽን ለመላክ ከ 2,000 በላይ የጭነት መኪኖች እንደሚያስፈልጉ  የስብሰባው ቃለ ጉባኤ ያሳያል።

እ.አ.አ. በ 1980 ዎቹ  በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረው ረሃብ ምስሎች ዓለም አቀፋዊ ጩኸት ካስከተሉ አስርት ዓመታት በኃላ ኢትዮጵያ በዓለም በፍጥነት እያደጉ ካሉ ኢኮኖሚዎች ውስጥ አንዷ ሆናለች፡፡ ድርቅ ፣ ግጭቶች እና የመንግስት ሁኔታዎችን መካድ ትግራይ ላስተናገደችው እና 1 ሚሊዮን የሚገመት ሰዎችን ገድሏል ለሚባለው ረሃብ አስተዋጽኦ አድርጓል ። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (እ.ኤ.አ.) በህዳር ወር በጦር ኃይላቸው እና የተግራይ ክልል መንግስት መካከል ጦርነትን መጀመሩን ባወጁ ጊዜ 5 ሚሊዮን ያህል የህዝብ ብዛት ያለው የትግራይ ክልል በአንበጣ ወረርሽኝ በመጠቃቱ የምግብ ዋስትና ችግር አጋጥሞት ነበር። የትግራይ መሪዎች ለሦስት አስርት ዓመታት ያህል ኢትዮጵያን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም አቢይ አህመድ ስልጣን ከተቆናጠጠ እና  በ 2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት ያስገኙለትን ማሻሻያዎችን ካስጀመረ በኋላ ተገለው ቆይተዋል::

በጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል። ከሃምሳ ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ሱዳን የተሰደዱ ሲሆን አንድ ዶክተር አዲስ መጤ ስደተኞች ላይ የረሃብ ምልክቶች በብዛት እንደሚታዩ ተናግረዋል።  ሌሎች አሁንም በረሃ ውስጥ ተሸሽገዋል፡፡ በቅርቡ ከትግራይ የወጣች አንዲት ሴት ከብቶች ፣ ፍየሎች እና ማጨድ የቻሉትን እህል ይዘው ከመጡ ሰዎች ጋር በዋሻ ውስጥ እንደቆየች ገልፃለች ፡፡

የአዲግራት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ጳጳስ በላኩት ደብዳቤ “በጦርነቱ መዘዝ እና በምግብ እጦት ሰዎች ሲሞቱ መስማት የየዕለት እውነታ ነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡

የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን በማከም ረገድ ወሳኝ የሆኑ ሆስፒታሎችና ሌሎችም ጤና ጣቢያዎች ወድመዋል ፡፡ በገቢያዎች ውስጥ ምግብ “አይገኝም ወይም እጅግ ውስን ነው” ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገልፅዋል።

ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኅዳር ላይ ሰራዊታቸው ድል መቀናጀቱን ቢያበስሩም ወታደራዊ እና ሌሎች አጋዥ ተዋጊዎቻቸው ለቀድሞው የክልሉ ባለስልጣናት መራራ ጠላት ከሆኑት የጎረቤት ኤርትራ ወታደሮች ጋር አሁንም ንቁ ሆነው በትግራይ ውስጥ ይገኛሉ ፡፡

ፍርሃት ብዙ ሰዎች ወደ ውጭ እንዳይወጡ አድርጓቸዋል፡፡ ሌሎች ደግሞ ይሸሻሉ፡፡ የትግራይ አዲስ ባለሥልጣናት ከ 2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን ተናግረዋል ፣ የአሜሪካ መንግሥት የሰብዓዊ ዕርዳታ ቢሮ ይህንን ቁጥር “አስደንጋጭ” ብሎታል፡፡ የተባበሩት መንግስታት እርዳታ የደረሰላቸው ሰዎች ቁጥር “እጅግ ዝቅተኛ” ነው ብሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ሬድዋን ሁሴን በትግራይ ያሉ ባልደረቦቻቸው ስላስተላለፉት የረሀብ ማስጠንቀቂያ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም ፡፡

በኤርትራ አቅራቢያ፣ በሰሜን ሽሬ አካባቢ እጅግ የከፋው ጦርነት የተካሄደበት ቦታ ሲሆን በአካባቢው እጃቸው ከተለካ ሕፃናት ውስጥ እስከ 10% የሚሆኑት ለከባድ አጣዳፊ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት መመርመሪያ መስፈርት ያሟሉ ሲሆን በርካታ ሕፃናትም ተጠቂ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት  ምንጭ አስታውቋል፡፡ በርካታ የሰብዓዊ እርዳታ ሠራተኞች ላይ የተጋረጠውን የተደራሽነት አደጋ በመግልፅ መረጃ ሰጪው ማንነታቸው እንዳይገለጥ ጠይቀዋል፡፡

በሽሬ ከተማ አቅራቢያ ባለፉት ዓመታት ከኤርትራ የተሰደዱ ወደ 100,000 የሚጠጉ ስደተኞችን የሚይዙ ካምፖች ይገኛሉ፡፡ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ሀሙስ እንዳሉት “ወደ ከተማ የገቡት ሰዎች ተዳክመዋል ማቅረብ ያልተቻለ እርዳታ በመለመን ላይ ናቸው” ብለዋል፡፡

ምግብ ዒላማ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በዩናይትድ ኪንግደም የተቋቋመ የጥናት ቡድን የሽሬ አካባቢን የሳተላይት ምስሎችን በመተንተን በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መጠለያ ግቢ ውስጥ ያሉ ሁለት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የመጋዘን ሕንፃዎች ተለይተው “ተደምስሰዋል”፡፡ የዲኤክስ  ኦፕን ኔትወርክ በማን እንደተደመሰሱ መለየት ባይችልም ቅዳሜ አዲስ ጥቃት መመዝገቡን ዘግቧል ፡፡

የግንኙነት መስመሮች ደካማ በመሆባቸው እና ጋዜጠኞች ከአካባቢው እንዲዘግቡ ስላልተፈቀደላቸው በትግራይ ውስጥ የሚፈጠሩ ክስተቶችን ማረጋገጥ እና ማስረጃ ማሰባሰብ እጅግ ፈታኝ ነው።

በአዲግራት ፣ በአድዋ እና በአክሱም ከተሞች “በደረስንባቸው ቦታዎች ሲቪሎች ላይ የሚደርሰው ጉዳት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው” ሲሉ የድንበር የለሽ ሐኪሞች የድንገተኛ ክፍል ባለስልጣን ቪኖሌስ ገልፀዋል፡፡ ውጊያን እና የጤና አገልግሎት እጥረቱንም ጠቅሰዋል፡፡ ረሃቡ “በጣም አሳሳቢ ነው” የውሃ እጥረትም ከፍተኛ ነው፡፡ ከ 140,000 በላይ ነዋሪ ያላት አዲግራት ከተማ ውስጥ ከ 21 የውሃ ጉድጓዶች መካከል አሁን የሚሰሩት ሁለቱ ብቻ በመሆናቸው ሰዎች ከወንዝ ውሃ እንዲጠጡ ተገደዋል፡፡ የንፅህና ጉድለተም በሽታን ይስከትላል፡፡ ቪኖሌስ “ከከተማው 10 ኪ.ሜ ያህል(6 ማይል) ርቆ ለወጣ የአደጋው ሙሉ ገፅታ ይታያል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ 

ያለ ምግብ የሰብአዊ እርዳታ ሠራተኞች የችግሩን መጠን ለመለካት ይቸገራሉ፡፡ በኢትዮጵያ የ “Action Against Hunger” ዳይሬክተር የሆኑት ፓኖስ ናቭሮዚዲስ “ከዋና አውራ ጎዳናዎች መጓዝ ባለመቻሉ አሁንም ልናገኛቸው ያልቻልናቸው ሰዎች ሁኔታ እንዴት የከፋ ሊሆን እንደሚችል ጥያቄ ያስነሳል” ብለዋል፡፡

ከግጭቱ በፊት የኢትዮጵያ ብሄራዊ አደጋ አስተዳደር አካል አንዳንድ የትግራይ ወረዳዎችን የምግብ ዋስትና እጥረት በመኖሩ ለእርዳታ ቅድሚያ ሰጥቷቸው ነበር ፡፡ ናቭሮዚዲስ እንዳሉት አንዳንዶቹ ቀድሞውኑ ከፍተኛ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የነበረባቸው ከሆነ ቀውሱ ከጀመረ ሁለት ወር ተኩል በኃላ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕፃናት እና እናቶች አፋጣኝ እርዳታ እንደሚፈልጉ መገመት አያዳግትም ብለዋል፡፡

በአሜሪካ በገንዘብ የሚደገፈው እና የሚተዳደረው የረሃብ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሲስተምስ ኔትወርክ እንዳለው በማዕከላዊ እና ምስራቃዊ ትግራይ ክፍሎች ከርሀብ በታች በሆነ የአስቸኳይ ጊዜ ምዕራፍ 4 ውስጥ እንደሚገኙ ግምት አለ፡፡የሚቀጥሉት ወራቶች በጣም ወሳኝ ናቸው ሲሉ በኢትዮጵያ የካቶሊክ የእርዳታ አገልግሎቶች ተወካይ ጆን ሹምላንስኪ ተናግረዋል፡፡  ቡድናቸው እስካሁን ድረስ ለ 70 ሺህ ይህል የትግራይ ሰዎች የሶስት ወር የምግብ አቅርቦት መስጠቱን ተናግረዋል ፡፡

ተዋጊዎች ረሃብን እንደ መሣሪያ ይጠቀማሉ ወይ ለሚለው ለእርዳታ ሰጪ ሰራተኞች በጣም አሳሳቢ ለሆነው ጥያቄ ሹምላንስኪ በኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል እና ፖሊስ ውድቅ ያደረጉት ሲሆን ሌሎች ጋር ያለውን እንደማያውቁ ተናግረዋል፡፡ “እነሱም በቂ ምግብ የላቸውም ብዬ አስባለሁ” ብለዋል፡፡

አስቸኳይ የሰብአዊ እርዳታ በትግራይ መዳረስ ለኢትዮጵያ የሰላም ጉዞ የመጀመሪያ እርምጃ ነው

የተለጠፈው በ 07/05/2013 የኤችአር / ቪፒ ብሎግ – በትግራይ ክልል ውስጥ የተነሳው ግጭት ከሁለት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሁኔታው ለአካባቢው ህዝብ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ከመሆኑም በላይ በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ክልል ያሉ ሁኔታዎችን እጅግ ተለዋዋጭ አድርጓቸዋል፡፡ እኔም ለኢትዮጵያ አመራር ግልፅ መልእክት አስተላልፌያለሁ ፤ እኛ ለመርዳት ዝግጁ ነን ፣ ነገር ግን ለሰብአዊ ዕርዳታ ሰጪዎች ተደራሽ መንገድ እስካልተገኘ ድረስ የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ መንግስት ያቀደውን የበጀት ድጋፍ መስጠት አይችልም ፡፡

የትግራዩ ደም አፋሳሽ ጦርነት እንደሚያስታውሰን ሆን ተብለው ግጭቶችን ለማብረድ እርምጃዎች ካልተወሰዱ ግጭቶች እየተባባሱ ይሄዳሉ፡፡ ከሁለት ወራት በፊት የውስጥ ጉዳይ ተብሎ የተጀመረው ጠብ ከክልልሉ እና ፌዴራል መንግሥቱ አልፎ መላውን ቀጠና እያናጋ ይገኛል፡፡ በመሬቱ ላይ ያለው ሁኔታ ግን ፍፁም ከውስጣዊ ‹የሕግ ማስከበር ዘመቻ› ያለፈ ነው፡፡ በዘር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፣ ግድያ ፣ ከፍተኛ ዘረፋ ፣ አስገድዶ መደፈር ፣ ስደተኞችን በኃይል መመለስ እና ሌሎች የጦር ወንጀሎች ሊሆኑ የሚችሉ ተግባሮች እየተፈፀሙ እንዳሉ ተደጋጋሚ ዘገባዎችን እየደረሱን ነው፡፡ ከ 2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከአካባብያቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ሰዎች በጣም ርዳታ በሚፈልጉበት ጊዜ ላይ ቢሆኑም በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ተደራሽነት እጅግ ውስን ነው ፣ ይህም የሰብዓዊ ዕርዳታን ለማድረስ በጣም ከባድ ያደርገዋል ፡፡
በመሬቱ ላይ ያለው ሁኔታ ግን ፍፁም ከውስጣዊ ‹የሕግ ማስከበር ዘመቻ› ያለፈ ነው፡፡ በዘር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፣ ግድያ ፣ ከፍተኛ ዘረፋ ፣ አስገድዶ መደፈር ፣ ስደተኞችን በኃይል መመለስ እና ሌሎች የጦር ወንጀሎች ሊሆኑ የሚችሉ ተግባሮች እየተፈፀሙ እንዳሉ ተደጋጋሚ ዘገባዎችን እየደረሱን ነው፡፡ ከ 2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከአካባብያቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ሰዎች በጣም ርዳታ በሚፈልጉበት ጊዜ ላይ ቢሆኑም በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ተደራሽነት እጅግ ውስን ነው ፣ ይህም የሰብዓዊ ዕርዳታን ለማድረስ በጣም ከባድ ያደርገዋል ፡፡ በተጨማሪም የግጭቱ መከሰት ለቀጠናውም ተርፏል፣ ለምሳሌ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የተሳተፉ ሲሆን የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሶማሊያ ወጥተዋል፡፡ 55,000 የሚሆኑ ስደተኞችም ወደ ሱዳን ተሰደዋል፡፡ በሱዳን እና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎችም አደገኛ ፍጥጫዎች እየተባባሱ ነው፡፡ ግጭቱ ሌሎች አገሮችን በማሳተፍ ወይንም ተጽዕኖ በመፍጠር ለአካባቢው መረጋጋት ሁሉ ቀጥተኛ ስጋት ሆኗል፡፡